ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን ከሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ጋር ውይይት አድርገዋል። በዚህ ወቅት የኢትዮጵያ እና ሩሲያን ዘርፈ ብዙ ግንኙነት በተመለከተ መሪዎቹ ውይይት አድርገዋል።
አቶ ደመቀ መኮንን እና የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ሀገራቱ በንግድ ፣ ኢኮኖሚ ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ማስፋት በሚቻልበት ዙሪያ መክረዋል። እንዲሁም በባህል እና በሰብዓዊ ጉዳዮች ግንኙነታቸውን ለማሻሻል ምክክር አድርገዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ ለሰርጌ ላቭሮቭ የፌዴራል መንግስት ህገ መንግስትን ለማስከበር በትግራይ ክልል ስለወሰደው እርምጃ ገለፃ አድርገዋል። ሩሲያ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እና ግዛታዊ አንድነት ለማክበር የማይናወጥ አቋም እንዳላት መረጋገጡትን ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው ላይ አንስተዋል።
Categories
More Stories
ኢዜማ የቀድሞው የአዲስ አበባ ም/ከንቲባ ታከለ ኡማ በህግ ሊጠየቁ ይገባል አለ
በቢጫ ለባሾቹ ምክንያት የእነ ጃዋር ችሎት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠበት
ሱዳናዊ ባለሀብት በአባይ ወንዝ ላይ 18 ኪሎ ሜትር ቦይ በመስራት 170 ሺህ ሄክታር መሬት በመስኖ ሊያለሙ ነው